ከቀናት በፊት የሱፐርሰፖርት ዩናይትዱ አሰልጣኝ ጋቪን ኸንተ ስለ አቡበከር ናስር የተናገሩት ንግግር አነጋጋሪ መሆኑ የሚታወቅ ነው።
አሰልጣኙ በንግግራቸው አበቡከር ናስር የት እንደሚገኝ እንደማያውቁ እና ለሁለት ሳምንታት ያህል ከቡድኑ ጋር አለመሆኑን ገልፀው ነበር።
ይህንንም በተመለከተ አቡበከር ናስር ከደቂቃዎች በፊት በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ምላሽ ሰጥቷል።
የአቡበከር ናስር ሙሉ ምላሽ “በሱፐርስፖርት ዩናይትድ እግር ኳስ ክለብ አሁን ያለሁበትን ሁኔታ በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎችን ተመልክቻለሁ፡፡ እውነት ለመናገር ከክለቡ ጋር የመረጃ ክፍተት ተፈጥሮ ነው እንጅ ጉዳዩ ይሄን ያክል የሚወራ አልነበረም፡፡”
- ማሰታውቂያ -
“በቅርቡ ማለትም በታህሳስ 27/2017 ባደረግነው የወዳጅነት ጨዋታ ላይ ባጋጠመኝ መጠነኛ ጉዳት ምክንያት በክለቡ የህክምና ቡድን ረፍት እንዳደርግ ተነግሮኝ በዛው መሰረት ረፍት አድርጌያለሁ፡፡”
“በኋላም የመቅረቴን ጉዳይ በተመለከተ ከወኪሌ መልእክት ተላከልኝ፡፡ ከዛም ለክለቤ ሁኔታውን አስረድቼ ለተፈጠረው የመረጃ ክፍተትም ይቅርታ ጠይቄያለሁ፡፡”


