በኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 10ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መካከል በወንድማማቾች ደርቢ ሲዳማ ቡና ድል ቀንቶታል፡፡
በመጀመሪያው እና በሁለተኛው አጋማሽ በተመጣጣኝ የጨዋታ ፍሰት በታየበት ጨዋታ 78 ደቂቃ ላይ ዳዊት ፍቃዱ ግልፅ ጎል ስቷል።ከዛ በዘለለ አመርቂ የሚባል ሙከራ ሁለቱም አላደረጉም ።
በ 90 + 2 ደቂቃ ላይ ለሲዳማ ቡና የተገኘችውን ፔናሊቲ አዲስ ግደይ መቶ የሀዋሳ ከተማ በረኛ አድኗት ኮርና ሊወጣ ችሏል፡፡ ከኮርና የተሻማችውን ኳስ ፔናሊቲዋን ያመከናት አዲስ ግደይ አስቆጥሮ 1-0 ሲዳማ ቡና አሸንፏል። በ ጨወታው 32.ዮሴፍ ዮሀንስ .፣58.ደስታ ዮሀንስ .፣92.አዲስ ግዴይ .የ ቢጫ ካርድ ሰለባ ነበሩ።
- ማሰታውቂያ -
የአሰልጣኞች አስተያየት
አለማየሁ አባይነህ ~ሲዳማ ቡና
” በልጆቼ ቁርጠኝነት አሸንፈናል አሁንም ይሄ ድል ይቀጥላል አሁን ለ ደረጃ ማሰብ እንጀምራለን”
አሰልጣኝ ውበቱ አባተ~ ሀዋሳ ከተማ
“አቻ ውጤቱ ለልጆቼ ጥሩ ነበረ።ግን ተሸንፈናል ብሆንም ልጆቼ ላይ ቅሬታ የለኝም፡፡ ጥሩ ተጫውተን ተሸንፈናል ቀጣይ ጨዋታ ላይ እናሻሽላለን።”




